NEWS DETAIL

News on 'በአማራ ክልል የሰብዓዊ ድጋፍና ሌሎች አቅርቦቶች ተደራሽ እንዲኾኑ የተግባቦት ሥራው እንዲጠናከ…'

በአማራ ክልል የሰብዓዊ ድጋፍና ሌሎች አቅርቦቶች ተደራሽ እንዲኾኑ የተግባቦት ሥራው እንዲጠናከር የሚጠይቅ መድረክ ተካሄደ።

ባሕር ዳር : ኅዳር 05/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ አዘጋጅነት የፌዴራል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን የሥራ ኃላፊዎች የክልል ሴክተር መሥሪያ ቤት መሪዎች እና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅት ተወካዮች የተገኙበት በሰብዓዊ ድጋፍና ሌሎች አቅርቦቶች ዙሪያ የሚመክር መድረክ በባሕርዳር ተካሂዷል፡፡ በመድረኩ የተገኙት የኢፌዴሪ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሳምሶን ቢራቱ በሰሜኑ ጦርነትና በውስጥ ግጭት ጉዳት የደረሰበት አማራ ክልል በርካታ ድጋፍ እንደሚያስፈልገው መገንዘባቸውን ገልጸዋል። የሰብዓዊ ድጋፍና ሌሎች አቅርቦቶች በተገቢው መጠንና ፍጥነት ተደራሽ እንዲኾኑ አጋር አካላት የበኩላቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል፡፡ የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ ጥላሁን መሃሪ (ዶ.ር) አስቸኳይ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች ቀበሌ ድረስ ወርደው ድጋፍ ማድረግ ለጀመሩ መንግሥታዊ ያልኾኑ ድርጅቶች ምሥጋና አቅርበዋል። ተቋማቱ ያደረጉት ድጋፍ ተመሳሳይ ተግባር መፈጸም ለሚፈልጉ ሁሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ያረጋገጠ ተግባር ነው ብለዋል። መልሶ ግንባታ እና አስቸኳይ ድጋፍ ተከታይነት ያለው እና የቅንጅት ሥራ ይፈልጋል ያሉት የፌዴራል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን ምክትል ዳይሬክተር ፋሲካው ሞላ በአማራ ክልል የሰብዓዊ ድጋፍና ሌሎች አቅርቦቶች ተደራሽ እንዲኾኑ የተግባቦት ሥራው እንዲጠናከር አሳስበዋል፡

Recent Posts

በአማራ ክልል የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመ…
Feb. 19, 2025
# በሶስት ክልሎች ተግባራዊ የሚሆን የ33 ሚ…
Feb. 19, 2025
የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ከፕሮጀክቶች ከዕቅድ…
Feb. 19, 2025
የካፒታል ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ችግር ያለበት ስ…
Feb. 5, 2025
የኦዲት ግኝት ያለባቸው ተቋማት እርምት እንዲወ…
Feb. 5, 2025
ተቋማት በኦዲት የተገኘባቸውን ጉድለት እንዲያር…
Feb. 5, 2025
የእርዳታና ብድር ሃብት አጠቃቀም ትኩረት ተሰ…
Feb. 5, 2025
በአማራ ክልል በጦርነቱ ምክንያት እየደረሰ ያለ…
Feb. 5, 2025
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በክልሉ በሰው ሰራ…
Feb. 5, 2025
የሙስና ትግሉ የሁሉንም ህብረተሰብ ርብርብ እን…
Feb. 5, 2025
ሰብዓዊ ድጋፍ ሰጭ ድርጅቶች በአማራ ክልል ለደ…
Feb. 5, 2025
በእርዳታና ብድር የሚመጣን ሃብት ለታለመለት አ…
Feb. 5, 2025
በፈፃሚ ተቋማት ላይ የተጠያቂነት ስርዓት ተግባ…
Feb. 5, 2025
ችግሮችን የሚፈታና በእውቀት ላይ የተመሰረተ ስ…
Feb. 5, 2025
የአማራ ክልል ምክር ቤት የተቋማትን ፋይናንስ …
Feb. 5, 2025
የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ለክልል ም/ቤት ቋሚ…
Feb. 5, 2025
#ቢሮው የ2017 በጀት ዓመት የእቅድ ኦረንቴሽ…
Feb. 5, 2025
The 2017 budget program has s…
June 19, 2024