NEWS DETAIL

News on 'በእርዳታና ብድር የሚመጣን ሃብት ለታለመለት አላማ ለማዋል ከመንግስት አስፈፃሚ አካላት ከፍተኛ…'

በእርዳታና ብድር የሚመጣን ሃብት ለታለመለት አላማ ለማዋል ከመንግስት አስፈፃሚ አካላት ከፍተኛ ሚና ይጠበቃል፡፡

ጥላሁን መሃሪ (ዶ/ር) የአብክመ ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ ************************* ገንዘብ ቢሮ ለክልል ም/ቤት የፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎችና አባላት በሰጠው ስልጠና የእርዳታና ብድር ሃብት ለታለመለት አላማ መዋሉን ለመከታተልና ለመቆጣጠር በዘርፉ የመጣው ሃብትና እየተከናወነ ያለውን አሰራር ለም/ቤት አባላቱ በውጪ ሃብትና በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት በኩል እውቀትን ሊያስጨብጥ በሚችል መልኩ የስልጠና ማንዋሎች ተዘጋጅተው ስልጠና ተሰጥቶባቸዋል፡፡ የገንዘብ ቢሮ ኃላፊ ጥላሁን መሃሪ (ዶ/ር) በስልጠናው እንደገለፁት በእርዳታና ብድር የሚገኘውን ሃብት ፈፃሚ ሴክተር መ/ቤቶች እንደመደበኛ በጀት በእቅድ ይዘው ለታለመለት አላማ እንዲውልና ማህበረሰቡን ተጠቃሚ እንዲያደርግ ከመንግስት አስፈፃሚ አካላት ከፍተኛ ሚና እንደሚጠበቅ ገልፀዋል፡፡ በእርዳታና ብድር የሚመጡ ሃብቶችና የሚተገበሩ ፕሮግራሞችና ፕሮጀክቶችን ሃብት በአግባቡ ለፈፃሚ አካላት በማስተላለፍ፣ የመጣውን ሃብት ለታለመለት አላማ መዋሉን በመከታተልና የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ብሎም የስራ ሪፖርቶችን በወቅቱ ለረጅና አበዳሪ አካላት የመላክና ተጨማሪ ሃብት ለማግኘት የሚሰራበትን መንገድ የውጭ ሃብት ግኝት ዳይሬክተሯ ወ/ሮ ሰብለወርቅ ሙላት በስልጠናው በዝርዝር አስረድተዋል፡፡ በሌላ በኩል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ማስተባበሪያ ዳይሬክተር አቶ አዝመራው ተጫኔ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሁለትና ከዛ በላይ የሆኑና በፈቃደኝነት የተመሰረተ የመንግስት አካል ያልሆኑና ለትርፍ ያልተቋቋሙ ከማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ነፃ ሆነው ለማህበረሰቡ ተጠቃሚነት የሚሰሩ መሆናቸውን ገልፀው በእነዚህ ድርጅቶች የመጣው ሃብት ለታለመለት አላማ እየዋለ ስለመሆኑ በመከታተልና በመገምገም ውጤታማ ስራ እንዲሰራ ጥረት እንደሚደረግ ዳይሬክተሩ አቶ አዝመራው ተናግረዋል፡፡

Recent Posts

በአማራ ክልል የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመ…
Feb. 19, 2025
# በሶስት ክልሎች ተግባራዊ የሚሆን የ33 ሚ…
Feb. 19, 2025
የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ከፕሮጀክቶች ከዕቅድ…
Feb. 19, 2025
የካፒታል ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ችግር ያለበት ስ…
Feb. 5, 2025
የኦዲት ግኝት ያለባቸው ተቋማት እርምት እንዲወ…
Feb. 5, 2025
ተቋማት በኦዲት የተገኘባቸውን ጉድለት እንዲያር…
Feb. 5, 2025
የእርዳታና ብድር ሃብት አጠቃቀም ትኩረት ተሰ…
Feb. 5, 2025
በአማራ ክልል በጦርነቱ ምክንያት እየደረሰ ያለ…
Feb. 5, 2025
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በክልሉ በሰው ሰራ…
Feb. 5, 2025
የሙስና ትግሉ የሁሉንም ህብረተሰብ ርብርብ እን…
Feb. 5, 2025
ሰብዓዊ ድጋፍ ሰጭ ድርጅቶች በአማራ ክልል ለደ…
Feb. 5, 2025
በፈፃሚ ተቋማት ላይ የተጠያቂነት ስርዓት ተግባ…
Feb. 5, 2025
ችግሮችን የሚፈታና በእውቀት ላይ የተመሰረተ ስ…
Feb. 5, 2025
የአማራ ክልል ምክር ቤት የተቋማትን ፋይናንስ …
Feb. 5, 2025
የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ለክልል ም/ቤት ቋሚ…
Feb. 5, 2025
በአማራ ክልል የሰብዓዊ ድጋፍና ሌሎች አቅርቦቶ…
Feb. 5, 2025
#ቢሮው የ2017 በጀት ዓመት የእቅድ ኦረንቴሽ…
Feb. 5, 2025
The 2017 budget program has s…
June 19, 2024