NEWS DETAIL

News on 'ሰብዓዊ ድጋፍ ሰጭ ድርጅቶች በአማራ ክልል ለደረሰው የሰባዊና ማህበራዊ ቀውስ አፋጣኝ ምላሽ እ…'

ሰብዓዊ ድጋፍ ሰጭ ድርጅቶች በአማራ ክልል ለደረሰው የሰባዊና ማህበራዊ ቀውስ አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጡ ተጠየቀ//

የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ በክልሉ መንግስትና የሲቪል ማህበርሰብ ድርጅቶች ጋር በክልሉ ለተከሰተው ሰው ሰራሽ እና የተፈጥሮ አደጋ ዙሪያ የሚመክር የአጋርነት መድረክ አካሄደ፡፡ በአማራ ክልል በሰሜኑ ጦርነት እና አሁን ላይ በተፈጠረውና አንድ ዓመት በላይ ባስቆጠረው ግጭት ምክንያት በገንዘብ ሊተመን የማይችል ሰብዓዊ ፣ ቁሳዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት መድረሱን በመድረኩ ጥናታዊ ጹሁፍ ያቀረቡት በአማራ ክልል በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎች መልሶ መቋቋምና ግንባታ ፈንድ ፅ/ቤት ስራ አስኪያጅ አባተ ጌታሁን (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ በክልሉ በተፈጠረው ጦርነት ለደረሰው ሰብዓዊ፣ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ አፋጣኝ ድጋፍ እንዲደረግ እና በችግሩ ስፋት ልክ ለአጋር አካላት በማሳወቅ በክልሉ የደረሰውንና እየደረሰ ያለውን ውድመት የሚመጥን ድጋፍ ማሰባሰብ እንደሚገባ አስታውቀዋል፡፡ አለማቀፍና አገር አቀፍ ሰብዓዊ ድጋፍ ሰጭ ድርጂቶች በአማራ ከሰሜኑ ጦርነት ጀምሮ ለደረሰው ማህበራዊ ፣ሰብዓዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ትኩረት ሰጥቶ እየደገፈን አይደለም ያሉት ዶክተር አባተ የአማራ ክልል ሰፊና ብዙ ህዝብ የሚኖርበት ክልል መሆኑን ጠቁመው ረጂ ድርጅቶች ለአማራ ክልል ህዝብ ችግሩን የሚመጥን አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጡ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡ ዶክተር አባተ አክለውም በዓለም ላይ ለጦርነት በትሪሊዮን የሚቆጠር ወጭ እንደሚወጣ ገልፀው ለመልሶ ግንባታ ስራ ግን በትሪሊዮን አይደለም በሚሊዮን እንኳን የሚቆጠር እንደማይሆን ተናግረዋል፡፡ በየትኛውም ዓለም በጦርነት የሚፈታ ችግር የለም ያሉት ስራአስኪያጁ የኛ ክልልም መጨረሻ ላይ መስማማት ላይ መድረሱ አይቀርምና በመልሶ መቋቋምና ግንባታ ስራውን የሰሜኑን ጦርነት ጨምሮ አሁን ላይ በክልሉ በደረሰው ጉዳት ልክ የሚመጥን ድጋፍ ለማድረግ መስራት እንደሚገባ አሰታውቀዋል፡፡

Recent Posts

በአማራ ክልል የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመ…
Feb. 19, 2025
# በሶስት ክልሎች ተግባራዊ የሚሆን የ33 ሚ…
Feb. 19, 2025
የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ከፕሮጀክቶች ከዕቅድ…
Feb. 19, 2025
የካፒታል ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ችግር ያለበት ስ…
Feb. 5, 2025
የኦዲት ግኝት ያለባቸው ተቋማት እርምት እንዲወ…
Feb. 5, 2025
ተቋማት በኦዲት የተገኘባቸውን ጉድለት እንዲያር…
Feb. 5, 2025
የእርዳታና ብድር ሃብት አጠቃቀም ትኩረት ተሰ…
Feb. 5, 2025
በአማራ ክልል በጦርነቱ ምክንያት እየደረሰ ያለ…
Feb. 5, 2025
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በክልሉ በሰው ሰራ…
Feb. 5, 2025
የሙስና ትግሉ የሁሉንም ህብረተሰብ ርብርብ እን…
Feb. 5, 2025
በእርዳታና ብድር የሚመጣን ሃብት ለታለመለት አ…
Feb. 5, 2025
በፈፃሚ ተቋማት ላይ የተጠያቂነት ስርዓት ተግባ…
Feb. 5, 2025
ችግሮችን የሚፈታና በእውቀት ላይ የተመሰረተ ስ…
Feb. 5, 2025
የአማራ ክልል ምክር ቤት የተቋማትን ፋይናንስ …
Feb. 5, 2025
የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ለክልል ም/ቤት ቋሚ…
Feb. 5, 2025
በአማራ ክልል የሰብዓዊ ድጋፍና ሌሎች አቅርቦቶ…
Feb. 5, 2025
#ቢሮው የ2017 በጀት ዓመት የእቅድ ኦረንቴሽ…
Feb. 5, 2025
The 2017 budget program has s…
June 19, 2024