NEWS DETAIL

News on 'የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በክልሉ በሰው ሰራሽና በተፈጥሮ አደጋ ለደረሰ ውድመት የሚያደርጉት…'

የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በክልሉ በሰው ሰራሽና በተፈጥሮ አደጋ ለደረሰ ውድመት የሚያደርጉት ድጋፍ በሚጠበቀው ልክ አለመሆኑ ተገለፀ

በአብክመ ገንዘብ ቢሮ በክልሉ በሰው ሰራሽና በተፈጥሮ አደጋ ለተጐዱ አካባቢዎች ድጋፍ ለማድረግ ከመንግስትና ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር ውይይት ተካሄደ፡፡ በምክክር መድረኩ የተገኙት የገንዘብ ቢሮ ኃላፊ ጥላሁን መሃሪ ዶ/ር ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በክልሉ ኮቪድን ጨምሮ በተለያዩ የሰላም ማጣት ምክንያቶች ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበትና ብዙ ቁጥር ያለው የማህበረሰብ ክፍልም የችግሩ ሰለባ እንደሆነ አንስተው በዚህም በእለት ደራሽና እርዳታ እንዲሁም በጤናና በትምህርት ተቋማቱ ላይ የደረሰውን ውድመት መልሶ የማቋቋም ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡ ቢሮ ኃላፊው ዶ/ር ጥላሁን አያይዘውም በዚህ ወቅት የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ድጋፍ ሲያደርጉ መቆየታቸውን ጠቅሰው አሁንም ክልሉ ችግር ውስጥ እንደሆነና የአለም አቀፍና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ከአሁን በፊት ከሚያደርጉት ድጋፍ በበለጠ ሃብታቸውን አጠናክረውና ተረባርበው የማህበረሰቡን ችግር በሚፈታ መንገድ ወደ ስራ እንዲገቡ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡ በክልሉ ከደረሰው ጉዳት አንፃር የሚመጥን ድጋፍ ለማሰባሰብና ጉዳቱ የበለጠ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራ ከማድረግ አኳያ ከዚህ መድረክ በተጨማሪ በክልል ደረጃና በአገር አቀፍ ደረጃም ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በተጨማሪ የተለያዩ አገራት ኤንባሲዎችና ረጅ ድርጅቶች በተገኙበት የአጋርነት መድረክ እንደሚካሄድም ቢሮ ኃላፊው ጨምረው ገልፀዋል፡፡ በክልሉ በተፈጠረው ጦርነት ምክንያት የደረሰው የጉዳት መጠን በደንብ መረዳትና ለማህበረሰቡ መረጃ መስጠት እንዲሁም ወደ ስራ ያልገቡ ሌሎች የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ወደ ስራ በመግባት ክልሉን ከጉዳት ለመታደግ መስራት እንዳለባቸው ተሳታፊዎች አንስተዋል፡፡

Recent Posts

በአማራ ክልል የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመ…
Feb. 19, 2025
# በሶስት ክልሎች ተግባራዊ የሚሆን የ33 ሚ…
Feb. 19, 2025
የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ከፕሮጀክቶች ከዕቅድ…
Feb. 19, 2025
የካፒታል ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ችግር ያለበት ስ…
Feb. 5, 2025
የኦዲት ግኝት ያለባቸው ተቋማት እርምት እንዲወ…
Feb. 5, 2025
ተቋማት በኦዲት የተገኘባቸውን ጉድለት እንዲያር…
Feb. 5, 2025
የእርዳታና ብድር ሃብት አጠቃቀም ትኩረት ተሰ…
Feb. 5, 2025
በአማራ ክልል በጦርነቱ ምክንያት እየደረሰ ያለ…
Feb. 5, 2025
የሙስና ትግሉ የሁሉንም ህብረተሰብ ርብርብ እን…
Feb. 5, 2025
ሰብዓዊ ድጋፍ ሰጭ ድርጅቶች በአማራ ክልል ለደ…
Feb. 5, 2025
በእርዳታና ብድር የሚመጣን ሃብት ለታለመለት አ…
Feb. 5, 2025
በፈፃሚ ተቋማት ላይ የተጠያቂነት ስርዓት ተግባ…
Feb. 5, 2025
ችግሮችን የሚፈታና በእውቀት ላይ የተመሰረተ ስ…
Feb. 5, 2025
የአማራ ክልል ምክር ቤት የተቋማትን ፋይናንስ …
Feb. 5, 2025
የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ለክልል ም/ቤት ቋሚ…
Feb. 5, 2025
በአማራ ክልል የሰብዓዊ ድጋፍና ሌሎች አቅርቦቶ…
Feb. 5, 2025
#ቢሮው የ2017 በጀት ዓመት የእቅድ ኦረንቴሽ…
Feb. 5, 2025
The 2017 budget program has s…
June 19, 2024