NEWS DETAIL

News on 'የእርዳታና ብድር ሃብት አጠቃቀም ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ ይገባል'

የእርዳታና ብድር ሃብት አጠቃቀም ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ ይገባል

የአብክመ ገንዘብ ቢሮ ከፈፃሚ ሴክተር መ/ቤት ኃላፊዎችና የፕሮጀክት ባለሙያዎች እንዲሁም ከእርዳታና ብድር ፕሮጀክትቶችና ፕሮግራሞች አስተባባሪዎች ጋር የእርዳታና ብድር የሃብት አጠቃቀምን ገምግሟል፡፡ የአብክመ ገንዘብ ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ አቶ አታላይ ጥላሁን በግምገማው እንደገለፁት ለክልሉ ከሚመደበው መደበኛ በጀት በተጨማሪ በእርዳታና ብድር ሃብት እንደሚመጣና ይህንን ሃብት የመጣለትን አላማ አውቆና በአግባቡ ይዞ ከመጠቀም አኳያ ከፈፃሚ ሴክተር መ/ቤቶች የትኩረት ማነስ እንዳለ ገልፀው ይህንን ክፍተት በመለየት በቀጣይ የተሻለ አሰራር በመፍጠር እንዲሁም የተሻለ የሃብት አስተዳደር እንዲኖር ታስቦ የተዘጋጀ ግምገማ መሆኑን አሳውቀዋል፡፡ ክልሉ አሁን ካለበት ችግር ውስጥም ሆኖ በእርዳታና ብድር በሚመጣው ሃብት እየተሰራ ያለው ስራ ጥሩ ነው ያሉት አቶ አታለይ ከዚህ በተሻለ በመስራትና እንደመደበኛ በጀት ሁሉ በእቅድ ይዞ ለታለመለት አላማ ማዋልና የጠራ መረጃ በመያዝ፣ ግልጽና አጭር ሪፖርት በወቅቱ በመላክ ተጨማሪ ሃብት በማምጣት የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ በግምገማው በገንዘብ ቢሮ አጠቃላይ የሴክተሮች አፈፃፀምና ከፈፃሚ ሴክተሮች ውስጥ የአብክመ መስኖና ቆላማ ቢሮ፣ የአብክመ ሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮና እንስሳትና አሳ ሃብት ልማት ጽ/ቤት ሪፖርታቸውን ለውይይት አቅርበዋል፡፡ በአብክመ ገንዘብ ቢሮ የውጭ ሃብት ግኝት ዳይሬክተሯ ወ/ሮ ሰብለወርቅ ሙላት በእርዳታና ብድር የሚመጣን ሃብት ፈፃሚ ሴክተር መ/ቤቶች ለተባለለት አላማ በመጠቀም በአሰራር የሚገጥሙ ችግሮችን በጋራ መፍትሔ በማበጀት የተሻለ ሃብት ለማምጣት ሁላችንም የበኩላችንን ኃላፊነት መወጣት ይገባናል ብለዋል፡፡

Recent Posts

በአማራ ክልል የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመ…
Feb. 19, 2025
# በሶስት ክልሎች ተግባራዊ የሚሆን የ33 ሚ…
Feb. 19, 2025
የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ከፕሮጀክቶች ከዕቅድ…
Feb. 19, 2025
የካፒታል ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ችግር ያለበት ስ…
Feb. 5, 2025
የኦዲት ግኝት ያለባቸው ተቋማት እርምት እንዲወ…
Feb. 5, 2025
ተቋማት በኦዲት የተገኘባቸውን ጉድለት እንዲያር…
Feb. 5, 2025
በአማራ ክልል በጦርነቱ ምክንያት እየደረሰ ያለ…
Feb. 5, 2025
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በክልሉ በሰው ሰራ…
Feb. 5, 2025
የሙስና ትግሉ የሁሉንም ህብረተሰብ ርብርብ እን…
Feb. 5, 2025
ሰብዓዊ ድጋፍ ሰጭ ድርጅቶች በአማራ ክልል ለደ…
Feb. 5, 2025
በእርዳታና ብድር የሚመጣን ሃብት ለታለመለት አ…
Feb. 5, 2025
በፈፃሚ ተቋማት ላይ የተጠያቂነት ስርዓት ተግባ…
Feb. 5, 2025
ችግሮችን የሚፈታና በእውቀት ላይ የተመሰረተ ስ…
Feb. 5, 2025
የአማራ ክልል ምክር ቤት የተቋማትን ፋይናንስ …
Feb. 5, 2025
የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ለክልል ም/ቤት ቋሚ…
Feb. 5, 2025
በአማራ ክልል የሰብዓዊ ድጋፍና ሌሎች አቅርቦቶ…
Feb. 5, 2025
#ቢሮው የ2017 በጀት ዓመት የእቅድ ኦረንቴሽ…
Feb. 5, 2025
The 2017 budget program has s…
June 19, 2024