NEWS DETAIL

News on 'የኦዲት ግኝት ያለባቸው ተቋማት እርምት እንዲወስዱ የመንግሥት ወጪ አሥተዳደር እና ቁጥጥር ቋሚ…'

የኦዲት ግኝት ያለባቸው ተቋማት እርምት እንዲወስዱ የመንግሥት ወጪ አሥተዳደር እና ቁጥጥር ቋሚ ኮሚቴ አሣሠበ፡፡

ደሴ: ታኅሣሥ 11/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ምክር ቤት የመንግሥት ወጪ አሥተዳደር እና ቁጥጥር ቋሚ ኮሚቴ የከፋ የኦዲት ግኝት አለባቸው ያላቸውን ተቋማት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመኾን በቀጣይ መደረግ በሚገባቸው አቅጣጫዎች ዙሪያ በኮምቦልቻ ከተማ ምክክር አድርጓል። ቋሚ ኮሚቴው የቃሉ ወረዳ፣ የኮምቦልቻ ከተማ አሥተዳደር ገቢዎች መምሪያ እና የቦሩ ሜዳ ጠቅላላ ሆስፒታል የኦዲት ግኝቶች ላይ ትኩረት አድርጓል። ለረጅም ጊዜ እየተንከባለለ የመጣ መሠብሠብ የነበረበት ገቢ መኖር እና መረጃ አለመስጠት ዋነኛ ችግሮች መኾናቸውን የየተቋማቱ የሥራ ኀላፊዎች በምክክሩ ተናግረዋል። የኦዲት ግኝቶችን የማስመለስ ሥራ እየተሠራ መኾኑን የገለጹት ኀላፊዎቹ ምክር ቤቱ ለጉዳዩ ትኩረት መስጠቱ በክልል ደረጃ ሊፈቱ የሚገባቸውን ችግሮች ለማቅረብ ምቹ ኹኔታን እንደፈጠረላቸውም አመልክተዋል፡ በአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ደሴ ማሥተባበሪያ ጽሕፈት ቤት በወንጀል የተገኘ ሐብት ማስመለስ የሥራ ሂደት ተጠሪ ይርጋ ደመቀ የሚሰጡ ጥቆማዎችን በማጣራት ጉድለት የፈጸሙ አካት ተጠያቂ እንድኾኑ ማድረግ እንደሚገባ ጠቅሰዋል፡፡ በአማራ ክልል ምክር ቤት የመንግሥት ወጪ አሥተዳደር እና ቁጥጥር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እመቤት ከበደ ውይይት በተደረገባቸው በሦስቱ ተቋማት እና በሌሎች በክልሉ የመንግሥት ተቋማት የኦዲት ግኝት መሠረት የተሰብሳቢ እና ተከፋይ የኦዲት ግኝት የክልሉን የፋይናስ ሥርዓት እያዛባ በመኾኑ ትኩረት እንደሚያስፈልገው አሳስበዋል። ግኝት ያለባቸው ተቋማትም በግኝቱ መሠረት እርምት ወስደው ግብረ መልስ መስጠት ይጠበቅባቸዋል ያሉት ሰብሳቢዋ ጉድለቱ ካልተስተካከለ የጥቆማ ኦዲት ተደርጎ ወደ ግለሰብ እንዲወርድ በማድረግ በሕግ ተጠያቂ እንዲኾኑ ይደረጋልም ሲሉ አብራርተዋል፡፡ አሚኮ

Recent Posts

በአማራ ክልል የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመ…
Feb. 19, 2025
# በሶስት ክልሎች ተግባራዊ የሚሆን የ33 ሚ…
Feb. 19, 2025
የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ከፕሮጀክቶች ከዕቅድ…
Feb. 19, 2025
የካፒታል ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ችግር ያለበት ስ…
Feb. 5, 2025
ተቋማት በኦዲት የተገኘባቸውን ጉድለት እንዲያር…
Feb. 5, 2025
የእርዳታና ብድር ሃብት አጠቃቀም ትኩረት ተሰ…
Feb. 5, 2025
በአማራ ክልል በጦርነቱ ምክንያት እየደረሰ ያለ…
Feb. 5, 2025
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በክልሉ በሰው ሰራ…
Feb. 5, 2025
የሙስና ትግሉ የሁሉንም ህብረተሰብ ርብርብ እን…
Feb. 5, 2025
ሰብዓዊ ድጋፍ ሰጭ ድርጅቶች በአማራ ክልል ለደ…
Feb. 5, 2025
በእርዳታና ብድር የሚመጣን ሃብት ለታለመለት አ…
Feb. 5, 2025
በፈፃሚ ተቋማት ላይ የተጠያቂነት ስርዓት ተግባ…
Feb. 5, 2025
ችግሮችን የሚፈታና በእውቀት ላይ የተመሰረተ ስ…
Feb. 5, 2025
የአማራ ክልል ምክር ቤት የተቋማትን ፋይናንስ …
Feb. 5, 2025
የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ለክልል ም/ቤት ቋሚ…
Feb. 5, 2025
በአማራ ክልል የሰብዓዊ ድጋፍና ሌሎች አቅርቦቶ…
Feb. 5, 2025
#ቢሮው የ2017 በጀት ዓመት የእቅድ ኦረንቴሽ…
Feb. 5, 2025
The 2017 budget program has s…
June 19, 2024