NEWS DETAIL

News on 'የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ከፕሮጀክቶች ከዕቅድ በላይ ሀብት ማግኘቱን አስታወቀ።'

የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ከፕሮጀክቶች ከዕቅድ በላይ ሀብት ማግኘቱን አስታወቀ።

ባሕር ዳር: ጥር 30/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በአማራ ክልል ምክር ቤት የበጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚከታተላቸውን ተቋማት የስድስት ወራት ሪፖርት ገምግሟል። በዚህም የገንዘብ ቢሮ አፈጻጸም ቀርቧል። የቢሮውን ሪፖርት ያቀረቡት የቢሮው ኀላፊ ጥላሁን መሐሪ (ዶ.ር) ከፌዴራል፣ ከውስጥ ገቢ፣ ከእርዳታ እና ሌሎች ገቢዎች የሚገኘው በጀት ተደልድሏል ብለዋል። የተመደበውን በጀትም ከፌዴራል እስከ ወረዳዎች በየደረጃው የማስተላለፍ ሥራ መሠራቱን ገልጸዋል። ከመንግሥት ግምጃ ቤት ከተመደበው መደበኛ በጀት 32 ነጥብ 19 ቢሊዮን ብር ወጭ ኾኖ ሥራ ላይ ውሏል። ለ77 ከተማ አሥተዳደር እና ለ138 መሪ መዘጋጃ ቤቶች 1 ቢሊዮን 458 ሚሊዮን ብር መመደቡንም ተናግረዋል። ወረዳዎች በጀታቸውን በአይቤክስ በመመዝገብ የማጠቃለል ሥራ 98 በመቶ ፈጽመዋል። ብድር የወሰዱ ወረዳዎች እና ከተማ አሥተዳደሮች በሙሉ ብድራቸውን መልሰዋል። የ28 ባለፕሮጀክት ቢሮዎችን የካፒታል በጀት አፈጻጸም የመከታተል እና የመደገፍ ሥራም ተሠርቷል። ለዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈጸሚያ ከ3 ነጥብ 02 ቢሊዮን ብር ውስጥ 0 ነጥብ 653 ቢሊዮኑ ገቢ ተደርጎ ለተጠቃሚ መሥሪያ ቤቶች ተላልፏል። የገጠር ልማታዊ ሴፍቲኔት በጀትም ለ82 ወረዳዎች መተላለፉን ጠቅሰዋል። በእርዳታ እና ብድር የተገዙ ቁሳቁሶች ለተጠቃሚ ተቋማት መገዛታቸውንም ገልጸዋል። ወደ ክልሉ ከሚገቡ አራት ፕሮጀክቶች መካከል ሁለቱ ተለይተዋል። ከቀረቡ 135 አዲስ ፕሮጀክቶች ውስጥ ከ123 ፕሮጀክቶች ጋር ስምምነት መደረጉን እና ከአዳዲስ ፕሮጀክቶች አምስት ቢሊዮን ብር ለማግኘት ታቅዶ 10 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር መገኘቱንም ገልጸዋል። ቴክኖሎጂን በመጠቀም ሥራዎችን ለማሳለጥ እየተሠራ መኾኑንም አመላክተዋል። በቋሚ ኮሚቴው የተሰጡ ግብረ መልሶች ተግባራዊ መደረጋቸውንም ገልጸዋል።

Recent Posts

በአማራ ክልል የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመ…
Feb. 19, 2025
# በሶስት ክልሎች ተግባራዊ የሚሆን የ33 ሚ…
Feb. 19, 2025
የካፒታል ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ችግር ያለበት ስ…
Feb. 5, 2025
የኦዲት ግኝት ያለባቸው ተቋማት እርምት እንዲወ…
Feb. 5, 2025
ተቋማት በኦዲት የተገኘባቸውን ጉድለት እንዲያር…
Feb. 5, 2025
የእርዳታና ብድር ሃብት አጠቃቀም ትኩረት ተሰ…
Feb. 5, 2025
በአማራ ክልል በጦርነቱ ምክንያት እየደረሰ ያለ…
Feb. 5, 2025
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በክልሉ በሰው ሰራ…
Feb. 5, 2025
የሙስና ትግሉ የሁሉንም ህብረተሰብ ርብርብ እን…
Feb. 5, 2025
ሰብዓዊ ድጋፍ ሰጭ ድርጅቶች በአማራ ክልል ለደ…
Feb. 5, 2025
በእርዳታና ብድር የሚመጣን ሃብት ለታለመለት አ…
Feb. 5, 2025
በፈፃሚ ተቋማት ላይ የተጠያቂነት ስርዓት ተግባ…
Feb. 5, 2025
ችግሮችን የሚፈታና በእውቀት ላይ የተመሰረተ ስ…
Feb. 5, 2025
የአማራ ክልል ምክር ቤት የተቋማትን ፋይናንስ …
Feb. 5, 2025
የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ለክልል ም/ቤት ቋሚ…
Feb. 5, 2025
በአማራ ክልል የሰብዓዊ ድጋፍና ሌሎች አቅርቦቶ…
Feb. 5, 2025
#ቢሮው የ2017 በጀት ዓመት የእቅድ ኦረንቴሽ…
Feb. 5, 2025
The 2017 budget program has s…
June 19, 2024